Friday, July 26, 2019

የቲራቮሎ ዋሻ" አዲስ መጽሃፍ

በአዲሳባ 
* በአይናለም መጻህፍት መደብር፡
* በሌሎች ምጽሃፍ መደብሮች፡
* ብሄራዊ ቴአትር በስተጀርባ፡
* እንዲሁም በአዙዋሪዎች እጅ ይገኛል።
በአስመራ 
አውገት እና ጋለሪ::

Wednesday, April 25, 2018

አትመንጥሩ አትመንጥሩ - ደኑን ስንላችሁ

"ለአማራ ህዝብ መብት መከበር እንታገላለን" የሚሉ ወገኖች የዶክተር አብይ አህመድን ስም ለማጠልሸት ሲተጉ አይቼ ገረመኝ። በጣም ገረመኝ። እውነት ለመናገር እሱ ራሱ የባህርዳር ስብሰባ ላይ እንዳለው ለአማሮችም ሆነ ለአንድነት ሃይሎች ከሰማይ የወረደላቸው በረከት ነበር። እጁን ብቻ ሳይሆን እግሩንም ስመው ቢቀበሉት ያዋጣቸዋል።

እነዚህ ፖለቲከኞች ኢትዮጵያዊ የነበረውን ዶክተር መረራ ጉዲና ገፍተው ገፍተው OLF -ኦሮሚያዊ አደረጉት። ዛሬ ላይ ቆም ብለን ስናየው፤ ኦቦ በቀለ፣ ዶክተር መረራ እና ኦቦ ዳውድ በአመለካከት ተቀራርበዋል። ሁኔታዎች በዚሁ ከቀጠሉ ተረኞቹ ለማና አብይ ናቸው።

እና አንድ የቆየ ግጥም ትዝ አለኝ። በመጠኑ ስትቀየር እንዲህ ትሆናለች። ትንቢት ሳይሆን ለእውነት የቀረበ...

አትመንጥሩ አትመንጥሩ - ደኑን ስንላችሁ
መረራ፡ በቀለ፡ አብይና ለማ - ኦነግ ሆኑላችሁ

ነብሩም አንበሳውም ጎሹም ሄደላችሁ